19/05/2025
በኢትዮጵያ የውጭ ዜጎች በሊዝ የመሬት ባለይዞታ እንዲሆኑ የሚፈቅድ የአዋጅ ረቂቅ በነገው ዕለት ለፓርላማ ሊቀርብ ነው
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መሬትን በሊዝ በባለቤትነት መያዝ የሚያስችላቸው የአዋጅ ረቂቅ፤ በነገው ዕለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሊቀርብ ነው። ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው ግለሰቦች በኢትዮጵያ መሬትን፣ የመኖሪያ ቤትን ወይም ተያያዥ ግንባታዎችን በባለቤትነት ለመያዝ፤ ቢያንስ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ሊመድቡ እንደሚገባ በአዲሱ አዋጅ ተደንግጓል።
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት “ባለቤት” ወይም “ባለይዞታ” የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣውን ይህን አዋጅ፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ተወያይቶ ለፓርላማ የመራው ከሁለት ሳምንት በፊት ነበር። አዋጁ የተዘጋጀው “የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት” ወይም “ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል መሬት የሚያገኙበትን” ህጋዊ አሰራር ለመዘርጋት እንደሆነ በመግቢያው ላይ ሰፍሯል።
“መኖሪያ ቤት” ማለት “ለግለሰብ ወይም ለቤተሰብ መኖሪያነት የሚያገለግል፤ ለንግድ ዓላማ ማዋል የማይፈቀድ ቤት” እንደሆነ በአዋጅ ረቂቁ የትርጓሜ ክፍል ላይ ተቀምጧል። ሆኖም ይህን መሰሉን ቤት “ለመኖሪያነት ዓላማ የማከራየት መብት የተጠበቀ” መሆኑን አዋጁ አመልክቷል።
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15956/