lij Aman

lij Aman እውነት ወደ ከፍታ ይወስዳል

ይህ ድርጊት መሀል አዲስ አበባ ገርጂ ወደ ዩኒቲ ዩኒቨርቲ መታጠፊያ መብራት ላይ አንዲት ሴት ዲዛየር መኪና እያሽከረከረች መጥታ ትቆማለች። ሁለት ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱ ሰዎች ሴትዮዋን ከ...
22/10/2025

ይህ ድርጊት መሀል አዲስ አበባ ገርጂ ወደ ዩኒቲ ዩኒቨርቲ መታጠፊያ መብራት ላይ አንዲት ሴት ዲዛየር መኪና እያሽከረከረች መጥታ ትቆማለች። ሁለት ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱ ሰዎች ሴትዮዋን ከመኪናዋ ጎትተው ከአስፓልት ወርውረው ከጣሉዋት በኋላ መኪናዋን ቀምተው ለማምለጥ ይሞክራሉ። በዚህ ጊዜ ትራፈክ ፖሊሱ ያይና ሳይረን እያስጮኸ በሞተር ይከተላቸዋል። የተደናገሩት ሌቦች ለማምለጥ በተቃራኒ አቅጣጫ ሲነዱ ከአንዲት ቪትዝ መኪና ጋር ይጋጫሉ። በዚህ ጊዜ ትራፊክ ፖሊሱ ይደርስና ግብግብ ይገጥማል።በአካባቢው ሰው ትብብር በቁጥጥር ስር ውለዋል። የተጎዳችው ባለ መኪናም ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች።

እነዚህን ዘራፊዎች በማየት በመከታተል አሳዶ ታግሎ በመያዝ የጀግና ተግባር የፈፀመው ትራፊክ ሽልማት ይገባዋል ምስጋናችን ይድረሰው።

ከሾፌሮች አንደበት

ኢናሊላሂ ወኢናኢለሂ ራጅዑን!ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ አመት በሞት ተለዩ።የህክምና እክል ደርሶባቸው ሲከታተሉ የነበረ ቢሆንም ከሞት መዳን አልቻሉም ሀገራችን ትልቅ አባት አታለች...
19/10/2025

ኢናሊላሂ ወኢናኢለሂ ራጅዑን!

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ አመት በሞት ተለዩ።
የህክምና እክል ደርሶባቸው ሲከታተሉ የነበረ ቢሆንም ከሞት መዳን አልቻሉም ሀገራችን ትልቅ አባት አታለች አላህ ጀነተል ፊርደውስን ይወፍቃቸው።

ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እመኛለሁ!

በእርግጥም በችግር ውስጥ ድል አለ!!!
11/10/2025

በእርግጥም በችግር ውስጥ ድል አለ!!!

11/10/2025

ጋዛውያኑ "ከራሳቸው መኖሪያ ቤት አስቀድመው የአላህን ቤት አፀዱ።" ይላል ዐቂል ዐዋዳ። ታዲያ እነዚህ ሰዎች እንዴት ሊሸነፉና ሊጠፉ ይችላሉ?
11/10/2025

ጋዛውያኑ "ከራሳቸው መኖሪያ ቤት አስቀድመው የአላህን ቤት አፀዱ።" ይላል ዐቂል ዐዋዳ። ታዲያ እነዚህ ሰዎች እንዴት ሊሸነፉና ሊጠፉ ይችላሉ?

09/10/2025
አልሃምዱሊላህ ፍልስጤምን የሚጠቅም ፊርማ ተፈርሟል።
09/10/2025

አልሃምዱሊላህ ፍልስጤምን የሚጠቅም ፊርማ ተፈርሟል።

" በጋዛ ጉዳይ ዝም አንልም" - የዩናይትድ ኪንግደም ተማሪዎች ነጃሺ ቲቪ መስከረም 28 / 2018"ስለጋዛ ዝም አንልም" ያሉት የዩናይትድ ኪንግደም ተማሪዎች  የመንግስትን ማስጠንቀቂያ በመስ...
08/10/2025

" በጋዛ ጉዳይ ዝም አንልም" - የዩናይትድ ኪንግደም ተማሪዎች

ነጃሺ ቲቪ መስከረም 28 / 2018

"ስለጋዛ ዝም አንልም" ያሉት የዩናይትድ ኪንግደም ተማሪዎች የመንግስትን ማስጠንቀቂያ በመስበር ለፍልስጤም ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት አደባባይ ወጥተዋል።

እስራኤል በጋዛ ላይ ያደረሰችውን የዘር ማጥፋት ጦርነት 2ኛ አመት ምክንያት በማድረግ እና እስራኤልን በመቃወም ለንደን ጨምሮ በአብዛሃኞቹ የእንግሊዝ ከተሞች ሰልፎች ተካሂደዋል።

የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር በእስራኤል ላይ የሚደረጉ ሰፊ ተቃውሞዎችን ለማርገብ የሰጡትን ማስጠንቀቂያ በመቃወም ሰልፍ የወጡት የዩኬ ተማሪዎች የጋዛን ጦርነት ሁለተኛ አመትን ምክንያት በማድረግ " ስለጋዛ በፍጹም ዝም አንልም" የሚል መፈክር ይዘው ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።

ለተቃውሞ የወጡት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩት ተማሪዎች የፍልስጤምን ባንዲራ በማውለብለብ እና “ከእንግዲህ ወራሪ የለም ፣ ፍትህ ያስፈልጋል ፣ ሰላም ለፍልስጤም ፣ ፍልስጤም ነፃ ናት ፣ ዝም አንልም” የሚሉ ፅሁፎችን ይዘው ነበር።

ተማሪዎቹ ከእስራኤል ጋር የሚደረግ ማንኛውም ግንኙነት በጋዛ የምትፈጽመውን የዘር ማጥፋት ጦርነት ማገዝ ነው ብለዋል።

ብሪታኒያ ከእስራኤል ጋር የምታደርገውን የንግድ ፣ ፖለቲካዊ እና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በአስቸኳይ በማቋረጥ በእስራኤል ላይ ለሚወሰድ ተግባራዊ እርምጃ ግንባር ቀደም መሆን አለባት ያሉት ለተቃውሞ የወጡት ተማሪዎች በተለይም ለብሪታኒያ ባለስልጣናት ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።

በብሪታኒያ ከተሞች ለተቃውሞ የወጡት ተማሪዎች "የፍልስጤማውያን ነፃነት በግልጽ እስካልታወጀ እና ነፃ ፣ ሉዓላዊነት እና ዲሞክራሲያዊት ፍልስጤም እስካልተመሰረተች ድረስ ዝም አንልም" የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወጣት ሙጅብ አሚኖ ፋኖ አሸባሪ ነው በማለት ተናግሯል የወጣት አሚኑ ንግግር ትክክል ነው ብላችሁ ታስባላችሁ
07/10/2025

ወጣት ሙጅብ አሚኖ ፋኖ አሸባሪ ነው በማለት ተናግሯል የወጣት አሚኑ ንግግር ትክክል ነው ብላችሁ ታስባላችሁ

07/10/2025
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በመካነ ሰላም ከተማ በመስጂድ ኑር በሃይማኖት አባቶች እና አገልጋዬች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በጽኑ አወገዘ!- ሀሩን ሚዲያ፥ መስከረም 26/2018ጉባኤው ...
06/10/2025

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በመካነ ሰላም ከተማ በመስጂድ ኑር በሃይማኖት አባቶች እና አገልጋዬች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በጽኑ አወገዘ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ መስከረም 26/2018

ጉባኤው ለሀሩን ሚዲያ በላከው መግለጫ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መስከረም 23/ 2018 በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ በመስጂድ ኑር ውስጥ በሃይማኖት አባቶች እና አገልጋዬች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ በጽኑ በማውገዝ የሃዘን መግለጫ በዛሬው ዕለት ማውጣቱን ገልጿል፡፡

📌 የሃዘን መግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡፦

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ መስከረም 23 ቀን 2018 በመስጂድ ኑር የተከሰተውን የሃይማኖት መሪዎች እና አገልጋዬች ግድያን የሰማነው በታላቅ ድንጋጤና ሀዘን ነው፡፡

የሃይማኖት መሪዎችን እና አባቶችን በመግደል የሚመጣ ምንም አይነት ሰላም እና ነፃነት የለም፡፡ ይህ አይነቱ ተግባር በፈጣሪ ዘንድ ታላቅ ፍርድ እና ቁጣ የሚያስከትል ከባድ ኃጢአት ሲሆን በምድርም መንግስታት ዘንድ ከባድ ፍርድ የሚያመጣ ጭካኔ የተሞላበት ወንጀል እንደሆነ ከልብ ልንገነዘበው ይገባል፡፡

ይህ ተግባር መሳርያ ባልታጠቁ ንፁኃን ዜጎች ላይ፤ ለዝያውም የሃይማኖት አባቶች እና አገልጋዮች ላይ፤ ከዚህም አለፍ ሲል መስጂድ ውስጥ በመግባት የተፈጸመ ድፍረት የተሞላበት አሰቃቂ ወንጀል በመሆኑ ሁሉም የሃይማኖት ተቋምት እና ሃይማኖተኛ ነኝ የሚል ዜጋ ሁሉ በአንድ ድምጽ ሊያወግዘው የሚገባ ተግባር ነው፡፡

ይህ አሰቃቂ እና ጭካኔ የተሞላበት ተግባር ለተፈጸመባቸው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዩች ጠቅላይ ምክር ቤት አባቶች እና አመራሮች በተለይም በመካነ ሰላም ለሚገኙ ሙስሊም ወገኖቻችን፣ ለሟችዎች ቤተ ሰቦች እና ወዳጆች በሙሉ ታላቁ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እና ጽናትን እንዲሰጥልን ከልብ እንማጸናለን።

© ሀሩን ሚዲያ

Address

Addis Ababa
000000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when lij Aman posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share